Skip to main content
news2
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፕላንና ልማት ቢሮ የቀድሞ አመራሮች አዲስ ከተሾሙት አመራሮች ጋር የትውውቅና የስራ ርክብክብ አደረጉ። ‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ የቀድሞ የስራ ኃላፊዎች አዲስ ከተሾሙት አመራሮች ጋር የትውውቅና የስራ ርክብክብ አድርገዋል። ‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በቅርቡ የአመራር ምደባና ሽግሽግ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ ‎በዚህም መሰረት አቶ ዳንኤል ዳምጠው የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑ ሲሆን የቀድሞ የተቋሙ ኃላፊ ዶክተር ባዩሽ ተስፋዬ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
‎እንዲሁም በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ ምክትል ኃላፊና የልማት መረጃ አስተዳደርና የስነ ህዝብ ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ ሆነው የተሾሙት ዶክተር ፈለቀች ተ/ማሪያም ከቀድሞ ኃላፊ አቶ አብርሃም ዓለሙ ጋር የስራ ርክብክብ አድርገዋል:: ‎በመርሀ-ግብሩ የቀድሞ የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ባዩሽ ተስፋዬ ለአዲስ አመራሮች ተቋሙ የሚያከናውናቸው ተግባራት ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል። ‎የቢሮው ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው ለተደረገላቸው ገለፃና አቀባበል አመስግነው በተቋሙ የተሰሩ ውጤታማ ተግባራት በመቀናጀት ማስቀጠል እንደሚገባ አመላክተዋል።
‎በመድረኩ የፕላንና ልማት ቢሮ ማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች ለተቋሙ አዲስ አመራሮች አቀባበልና ለቀድሞ አመራሮች የሽኝት መርሀግብር በማካሄድ ለቀድሞ አመራሮችና አዲስ ለተሾሙት አመራሮች መልካም የሥራ ጊዜን ተመኝተዋል።